የሠላት ማዕዘናት ግዴታዎች

የሠላት ማዕዘናት የሚባሉት የሠላት ዋና ዋና ክፍሎች ሲሆኑ ታውቆም ሆነ በመርሳት ከተተዉ ሠላት የሚበላሽባቸው ነገሮች ናቸው፡፡

እነርሱም የሚከተሉት ናቸው፡

ተክቢረቱል ኢሕራም (የመግቢያ ተክቢራ ወይም ‹‹አላሁ አክበር‹‹) • መቆም ለሚችል ሰው መቆም • ከተከታይ ወይም ማእሙም በስተቀር ፋቲሐን ማንበብ፤ • ሩኩዕ፤ • ከሩኩዕ ቀና ማለት፤ • ሱጁድ፤ • በሁለት ሱጁዶች መሐከል መቀመጥ፤ • የመጨረሻው ተሸሁድ፤ • ለመጨረሻው ተሸሁድ መቀመጥ፤ • መረጋጋት ወይም ጡመእኒና እና ማሰላመት ናቸው

ሰላት ግዴታዎች ማለት በሰላት ውስጥ ግዴታ የሆኑ አካላት ማለት ሲሆን እነዚህ ግዴታዎች ቢሆን ተብሎ ከተተው ሰላቱ ይበላሻል። ነገር ግን አንድ ሰው ረስቶ ወይም ዘንግቶ ከተዋቸው የጐደለውን ለመሙላት የመርሳት ሱጁድ የመውረድ ግዴታ አለበት። ይህም ወደፊት በሚወጣው ርዕስ የምንመለከተው ይሆናል።

የሰላት ግዴታዎች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡

ከተክቢረተል ኢሕራም ውጭ ያሉት ሁሉም ተክቢራዎች፤ • ሩኩዕ ላይ እያሉ አንድ ጊዜ ‹‹ሱብሐነረቢየል ዐዚም›› ማለት፤ • ብቻውን ለሚሰግድና ኢማም ሆኖ ለሚያሰግድ ‹‹ሰሚዐላሁ ሊመን ሐሚደሁ›› ማለት፤ • ለሁሉም ሰጋጅ ‹‹ረበና ወለከልሐምዱ›› ማለት፤ • ሱጁድ ውስጥ አንድ ጊዜ ‹‹ሱብሐነ ረቢየል አዕላ›› ማለት፤ • በሁለቱ ሱጁዶች መሐከል ሲቀመጡ አንድ ጊዜ ‹‹ረቢግፊርሊ›› ማለት፤ እና • የመጀመሪያው ተሸሁድ፤ ናቸው፡፡ እነኚህ ግዴታዎች በመርሳት ምክንያት ከተተዉ ግዴታነታቸው ይቀራል፡፡ እነርሱም የእርሳና ሱጁድ ወይም ሱጁደ ሰህው በማድረግ ይጠገናሉ፡፡

የሠላት ውስጥ ሱናዎች፡ ማንኛውም የሠላት ማዕዘን ወይም ግዴታ ውስጥ የማይመደብ ንግግርም ሆነ ተግባር የሠላት ውስጥ ሱና ይባላል፡፡ ሠላትን የሚያስውብና የሚያሟላ ነው፡፡ በመሆኑም እርሱን በዘውታሪነት መፈፀም ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን እርሱን በመተዉ ሠላት አይበላሽም፡፡