እባኮትን በመቀበል የስራችንን ማስቀጠል እና ማደግ ለማድረግ እርዳን። አላህ ይስጥዎት።
የወለድ ፍርድ
ወለድ በጥብቅ የተከለከለ እርም(ሐራም) ነው፡፡ እርምነቱም በግልጽ የቁርኣን አንቀጾችና ሐዲሶች ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ ወለድ ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል አንዱ ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ከወንጀለኞች መካከል ጦርነትን እንዳወጀበት የዛተው ወለድን በሚበላና በርሱ በሚገለግል ሰው ላይ ብቻ ነው፡፡ የወለድ እርምነት በኢስላም ብቻ ሳይሆን በቀደምት መለኮታዊ መመሪያዎችም ጭምር የተደነገገ ነው፡፡ ነገር ግን ከቁርኣን ውጭ ባሉ መመሪያዎች ውስጥ ያሉት ሕግጋት ድለዛና ክለሳ እንደተደረገባቸው ሁሉ የወለድ ሕግም ተመሳሳይ ነገር አጋጥሞታል፡፡ አላህ (ሱ.ወ) የመጽሐፍቱ ባለቤት የሆኑትን ሕዝቦች የቀጣበትንና በነርሱ ላይ የተቆጣበትን ምክንያት ሲገልጽ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ከርሱ በርግጥ የተከለከሉ ሲሆኑ አራጣንም በመያዛቸውና የሰዎችን ገንዘቦች ያለ አግባብ በመብላታቸው ምክንያት (ረገምናቸው)፡፡›› (አል ኒሳእ 161)
